ረጅም ዓመት ያገለገሉ "አሮጌ" ተሽከርካሪዎች ከአገልግሎት ውጭ የሚደረጉት በበካይ ጋዝ ልቀት መጠናቸው እንጂ፤ በአገልግሎት ዘመናቸው መርዘም እንዳልሆነ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ፣ ረጅም ዓመት ያገለገሉ "አሮጌ" ተሽከርካሪዎች ከአገልግሎት ውጭ የሚደረጉት ከሚገባው በላይ ጭስ በማውጣት የአየር ብክለት ሲፈጥሩ እንጂ፤ በአገልግሎት ዘመናቸው መርዘም አይደለም ብሏል።
የቢሮው የሞተር አልባ ትራንስፖርት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሳሙኤል እንደገለጹት፣ "አሮጌ" ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ ከአዲስ አበባ ሊወጡ ነው ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ የተዛባ ነው።
ዳይሬክተሩ አቶ ግርማ በማብራሪያቸው፤ በምርመራ ወቅት የ2017 ዓ.ም. ሞዴል ሆኖ መስፈርቱን ባለማሟላቱ የወደቀ እንዲሁም የ1998 ዓ.ም. ሞዴል ሆኖ አልፎ አገልግሎት ላይ የዋለ ተሽከርካሪ መኖሩን አስረድተዋል።
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች አስፈላጊው ጥገና ተደርጎላቸው ደረጃውን አሟልተው ከተገኙ አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ነገር ግን ከከተማው እድገት ጋር የማይሄዱና እድሜ ጠገብ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ደረጃ በደረጃ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የመተካት ሥራ ይከናወናል።
ከተሽከርካሪ የሚወጣ በካይ ጋዝ ልቀት ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1051/2017 ማንኛውም ተሽከርካሪ የጸደቀውን የልቀት ደረጃ የማሟላት ግዴታ እንዳለበት ይደነግጋል።
ደረጃውን ያላሟሉ ተሽከርካሪዎች ልቀትን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን እንዲሁም የነዳጅና የአየር ማጣሪያ ሲስተሞችን መጠቀም እንደሚገባቸውም መመሪያው ያዛል።
#afromekina
Loading content...
