ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ፣ ጅማ፣ ደብረ ማርቆስ እና ነቀምቴ የሚዘልቁ የፍጥነት መንገዶች የአዋጭነት ጥናት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ የመንገድ መረብ ባለፉት 8 ዓመታት በ53,000 ኪ.ሜ ማደጉን እና በቀጣይ 5 ዓመታት 245,000 ኪ.ሜ ለማድረስ ዕቅድ መያዙን የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል፡፡
በተጨማሪም በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የሀገሪቱን የፍጥነት መንገዶች ርዝመት ወደ 1,600 ኪሎ ሜትር ለማሳደግ ታቅዶ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ፣ ጅማ፣ ደብረ ማርቆስ እና ነቀምቴ የሚዘልቁ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶች የአዋጭነት ጥናት መጠናቀቁንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ቁልፍ መረጃዎች፦
🛣 የመንገድ እድገት፦ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 126,773 ኪ.ሜ በ2018 ዓ.ም አጋማሽ ወደ 180,232 ኪ.ሜ አድጓል፡፡ ባለፉት 8 ዓመታት +53,000 ኪ.ሜ አዲስ መንገድ ተገንብቷል።
🚗 የፍጥነት መንገዶች፦ ከ2010 ዓ.ም በፊት የነበረው ሽፋን 84.7 ኪ.ሜ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ የሞጆ-መቂ-ባቱ-አርሲ ነገሌ እና ድሬዳዋ-ደዋሌ አዳዲስ የፍጥነት መንገዶች (+450 ኪ.ሜ.) ተገንብተዋል፡፡
🏗 የፕሮጀክቶች አፈጻጸም፦ ባለፉት 8 ዓመታት 182 ፕሮጀክቶች ወደ ግንባታ የገቡ ሲሆን 71 ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለትራፊክ ክፍት ሆነዋል።
#afromekina
Loading content...
