በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸውን እንዲቀንሱ መረጃ የሚሰጥ የቀለም ማንቂያ እየሰራ ነው
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸውን እንዲቀንሱ መረጃ የሚሰጥ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የቀለም ማንቂያ ጉብታ እየሰራ ይገኛል፡፡
የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት እና ኮምኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ዲባባ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነዉ የአሽከርካሪ ማንቂያና ፍጥነት መቀነሽ እና ቀለም ቅብ ስራ እያከናወነ ያለው በፍጥነት ሳቢያ ተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋ ይደርስባቸዋል ተብለው በጥናት በተለዩ ቁልቁለታማ ቦታዎች፣ መጋጠሚያ አካባቢዎች፣ ወደ አደባባይ መግቢያ ስፍራዎች፣ የትራፊክ መብራት በሌለባቸው መስመሮች ላይ ነው፡፡
ይኸው የአሽከርካሪ ማንቂያ ቀለም ተግባራዊ ከተደረጉባቸው ቦታዎች መካከል ፒያሳ፣ ከሜክሲኮ ወደ ሳርቤት፣ አጫሉ መንገድ፣ ከለቡ መብራት እስከ ለቡ መድኃኒዓለም፤ አድዋ ሙዚየም፣ ቤተ መንግስት አካባቢ፤ ከካዛንቺስ - ሴቶች አደባባይ፤ ከካዛንቺስ ወደ ቤተመንግስት በሚወስደው መንገድ ላይ፣ ከቤተ-መንግስት- ቴዎድሮስ አደባባይ፣ ከአብርሆት ቤተ መጽሃፍት ወደ ቀይ ባህር ኮንዶሚኒየም፣ የወንዝ ዳር ፕሮጅክቶችን የሚያቋርጡ መንገዶችን ተከትሎ በተዘጋጁ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች ላይ ነው።
በተለይም የቀለም ቅብ ስራው አሽከርካሪዎች እንደ የመንገዱ የፍጥነት ወሰን እንዲያሽከረክሩ እና ከፊት ለፊታቸው ያለውን የመንገድ ሁኔታ እንዲያውቁ፤ ቦታው ሲደርሱም ልዩ ትኩረት በመስጠት እንዲያሽከረክሩ ብሎም ለእግረኞች ቅድሚያ እንዲሰጡ የሚረዳ ነው።ማንቂያ የተለያየ ቀለም በመቀባት የአሽከርካሪውን እይታ ከመጨመርም አልፎ ንዝረትን በመፍጠር ፍጥነትን የመቀነስ ባህሪ ያለው ሲሆን አሽከርካሪውም ካለበት ሁኔታ ነቅቶ እንዲያሽከረክር የሚያግዝ ነው።
#afromekina
Loading content...
