ጥናት እንደሚያመለክተው የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪዎች ከነዳጅ ተሽከርካሪዎች ሞተር የበለጠ ረጅም ዕድሜ አላቸው
በዩናይትድ ስቴትስ የተካሄደ አዲስ ጥናት እንዳረጋገጠው፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EV) የሚጠቀሙባቸው ዘመናዊ ባትሪዎች በአሜሪካ መንገዶች ላይ ከሚገኙት አብዛኛዎቹ የነዳጅ ሞተር መኪኖች ዋና ዋና አካላት (ሞተር እና ማስተላለፊያ) የበለጠ ረጅም የአገልግሎት ዘመን አላቸው። ይህ መረጃ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ዘላቂነት እና የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት አስተማማኝነት በተመለከተ ሲነሱ ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥ ነው።
የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው፣ አብዛኛዎቹ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራቾች ለዋና ባትሪዎቻቸው እስከ 8 ዓመት ወይም 160,934 ኪሎሜትር ድረስ ዋስትና ይሰጣሉ። ይህም ባትሪው ከዚህ ጊዜ በኋላም ቢሆን ቢያንስ 70% የሚሆነውን የመጀመሪያ አቅሙን ይዞ መቆየቱን ያረጋግጣል። የባትሪ አቅም ከጊዜ በኋላ ትንሽ እየቀነሰ ቢሄድም ፣ ይህ የመቀነስ መጠን እጅግ ዝቅተኛ በመሆኑ ተሽከርካሪው ከአገልግሎት ውጪ እስኪሆን ድረስ ባትሪው ዋናውን ሚና መጫወት ይችላል፡፡
በአንጻሩ፣ በርካታ የነዳጅ መኪኖች በዋናነት ውስብስብ በሆኑት የሞተር እና የማስተላለፊያ ክፍሎች ብልሽት ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ ይሆናሉ። የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሞተር እና ማስተላለፊያ ስርዓቶች እጅግ በጣም አናሳ ክፍሎችን የሚጠቀሙ በመሆናቸው፣ ለመበላሸት ያላቸው ዕድል በእጅጉ የቀነሰ ነው። ይህ ደግሞ አጠቃላይ የተሽከርካሪውን የዕድሜ ዘመን ከፍ ያደርገዋል ተብሏል።
በአማኑኤል አክሎግ
#afromekina
Loading content...
