የነዳጅ ድጎማ ሙሉ በሙሉ ሊቆም ነው ተባለ
መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ፣ እስከ መጪው የካቲት 2018 ዓ.ም. መጨረሻ ድረስ ከድጎማ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚወጣ ካፒታል ያገኘዉ መረጃ አመልክቷል።
ይህ ውሳኔ መንግሥት ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር በገባው ቃል መሠረት የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተግባራዊ ለማድረግ የወሰደው እርምጃ አካል መሆኑ ለመረዳት ችሏል።
ባለሥልጣናቱ በገቡት ቃል መሠረት በዚህኛው የታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ አዲስ የዋጋ ጭማሪ ተግባራዊ አድርገዋል። በዚህም መሠረት ለተጠቃሚዎች የሚቀርበው የናፍጣ ዋጋ በ11 በመቶ፣ የቤንዚን ዋጋ ደግሞ በ5 በመቶ እንዲጨምር ተደርጓል።
#afromekina
Loading content...
