በደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚካሄድ የደረሰኝ ቁጥጥር ተጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ የሚገቡ፣ከከተማዋ የሚወጡና በከተማዋ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፣ሚኒባሶችና አነስተኛ ሽፍን መኪኖች ላይ የመኪና ኦፕሬሽን ስራዎች ማጠናከሩን አስታውቋል ፡፡
በዚህም ያለደረሰኝ የሚካሄድ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የህግ ተጠያቂነት በአሸከርካሪዎች ላይ ጭምር እንዲሰፍን እያደረገ መሆኑን ቢሮው ጠቅሷል፡፡
በአሁኑ ወቅት የደረሰኝ ቁጥጥሩ በቀን ብቻም ሳይሆን በለሊት ጭምር ተጠናክሮ መቀጠሉ ያሳወቀ ሲሆን ደረሰኝ ሳይዙ ሸቀጦች ይዘው በተንቀሳቀሱት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ወስጃለው ብሏል።
ቢሮው የቁጥጥር ስራውን በየደረጃው ከተቋቋሙ ግብረ ሀይሎች ጋር በመቀናጀት እያከናወነ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን ፤ በዚህም ተሸከርካሪዎች ዕለታዊ ደረሰኝ ሳይዙ በከተማዋ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ፣ከከተማው ሲወጡ ተገኝተው አስተዳደራዊ የቅጣት እርምጃ ከመውሰድ በተጨማሪ ለእያንዳንዱ ለጫኑት ሸቀጥ ደረሰኝ እንዲቆርጡ ተደርጓልም ሲል ገልጾል፡፡
በቀጣይም በከተማዋ ጭነት የጫኑ ማንኛውም አይነት ተሽከርካሪዎች፣ ለጫኑት ሸቀጥ ደረሰኝ እንዲቆርጡ ብቻም ሳይሆን አሽከርካሪዎቻቸው ላይም የህግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን የሚደረግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
#afromekina
Loading content...
