ከቦሌ ኤርፖርት ወደ ጎሮ የሚወስደው መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀን ያህል በከፊል ዝግ ነው ተባለ
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከቦሌ ኤርፖርት ወደ ጎሮ የሚወስደው መንገድ የመጨረሻ ደረጃ ተደራራቢ አስፋልት የማልበስ ስራ እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በዚህም ምክንያት ከህዳር 15 ጀምሮ ለሦስት ቀናት ያህል ከቦሌ አቅጣጫ ወደ ጎሮ ሚወስደው የመንገዱ ክፍል በከፊል ለትራፊክ ዝግ ይሆናል ሲሉ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የጥገና ስራው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ መንገዱ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ዝግ በመሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አሳስቧል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 4 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 60 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡
#afromekina
Loading content...
