የነዳጅ ዋጋ ከሦስት ዓመት በኋላ በበርሜል 100 ዶላር ተሻገረ
በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት የምርት እና የትራንስፖርት መስመሮችን በማስተጓጎሉ፣ የነዳጅ ዋጋ ባለፉት ሦስት ዓመታት ተኩል ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ 100 ዶላር ተሻገረ። የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ይህንን ታሪካዊ ጣሪያ የነካው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአቅርቦት እጥረት ሊከሰት ይችላል የሚለው ስጋት በመኖሩ ነው።
ግጭቱ በዋና ዋና የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የጸጥታ ስጋት መፍጠሩን ተከትሎ፣ የኢኮኖሚ ተንታኞች የዋጋ ግሽበት ሊባባስ እንደሚችል እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
ሁኔታው በአፋጣኝ የማይረግብ ከሆነ፣ የነዳጅ ዋጋ ይበልጥ ሊጨምር እንደሚችል ይጠበቃል።
በአማኑኤል አክሎግ
#afromekina
Loading content...
